ባሕር ዳር: የካቲት 26/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ዙሪያ ገባው በታሪክ ተከቧል፣ በቅዱስ መንፈስ ተሞልቷል፡፡ በሠርክ የአምላክ ስም ይነሳበታል፣ ገናናነቱ ይነገርበታል፣ ምስጋና ይቀርብበታል፣ ኪዳን እየተደረሰ ቅዳሴ እየተቀደሰ ለምድር በረከት ይለመንበታል፡፡ ጉባኤ ተዘርግቶ ሊቃውንቱ ምስጢር ያመሰጥሩበታል፣ ደቀመዛሙርቱ ከአበው ግርጌ ተቀምጠው እውቀት ይገበዩበታል፡፡ ሊቃውንት እየዘመሩበት፣ ደቀመዛሙርት እየቀጸሉበት፣ መነኮሳት ዳዊት እየደገሙበት፣ መቁጠሪያቸውን እየቆጠሩ የአምላክን ስም እየጠሩበት፣ ለምድር ጸጋውን እየለመኑበት፣ ምዕምናን […]
Source: Link to the Post