
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጥናት አጥንቶ በማዕከል፣በክ/ከተማ እና ወረዳ በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች እና በሜሪት ደረጃ ለተሸሞ ዳይሬክተሮችና ቡድን መሪዎች የሚገባ ጥቀማ ጥቅም ፓኬጅ ከጥር 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ይፋ መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡
የመስተንግዶ ወርሃዊ ወጪ ወደ ተቋሙ ለሚመጡ እንግዶች እና ለተፈቀደላቸው አመራሮች የሻይ፣ቡና እና ለተለያዩ መስተመንግዶ ወጪ ብቻ የተፈቀደለት ቢሆንም በአንድ አንድ ክ/ከተሞች እና ወረዳዎች ይህንን የመስተንግዶ በጀት ወደ ብር በመቀየር እየወሰዱ መሆኑን ጣብያችን ለማወቅ ችሏል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ሌሎች ክ/ከተሞችና ወረዳዎች ላይ በብር እየቀየሩ እየወሰዱት እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የከተማ አስተዳደሩም በዚህ ተግባር ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ አመራሮች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ማሳሰቡንና ከዚህ በኃላ በድርጊቱ ተሳትፈው የሚገኙት ላይ እርምጃ እወስዳለው ማለቱን ሰምተናል፡፡
በአቤል ደጀኔ
መጋቢት 08 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን
Source: Link to the Post