
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት ኢትዮጵያን ሊያፈርስ እየሰራ ነው መባሉ እንደ ቀልድ እንደሚመለከቱት ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት መጋቢት 19/2015 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥትን የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ነው። በዛሬው 11ኛ የፓርላማ መደበኛ ስብሰባ “መንግሥት አገርን ሊያፈርስ ነው በማለት በርካቶች ላይ ጥርጣሬ ተፈጥሯል” በማለት የጠየቁት የምክር ቤቱ አባል አቶ ጀምበር አያልነህ ናቸው።
Source: Link to the Post