የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ቦታዎች የተፈጸሙ ጥቃቶች በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀሎች ናቸው ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አመለከተ። ኮሚሽኑ እንዳለው ለወራት ክስተቱን በተመለከተ ባደረገው ምርመራ መሰረት ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ “በጥቃቱ በተሳተፉ ሰዎችና ቡድኖች በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል ባሕርያትን የሚያሟሉ ናቸው” ብሏል።
Source: Link to the Post