
መንግስታዊ አፈናው ተጠናክሮ ቀጥሏል፤ የአማራ ወጣቶች፣ የአሻራ ሚዲያ እና የንስር ሚዲያ ጋዜጠኞች በባህር ዳር መታሰራቸው ተገልጧል። አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ ግንቦት 11 ቀን 2014 ዓ.ም አዲስ አበባ ሸዋ የአሻራ ሚዲያ እና የንስር ሚዲያ ጋዜጠኞች እና ሌሎች የሚዲያው አባላት በአፋኙ መንግስት ግንቦት 11/2014 በስራ ላይ እያሉ በባህር ዳር በግፍ ታፍነው መወሰዳቸው ተገልጧል። አማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) ያነጋገረው የዐይን እማኝ የአማራ ወጣቶች ማህበር ሰብሳቢ ኃይለ ሚካኤል ባይህ በባህር ዳር ቀበሌ 4 አዴት ተራ አካባቢ ከሚገኘው የንስር እና የአሻራ ሚዲያ ስቱዲዮ በርካታ ጋዜጠኞችን አፍነው ወዳልታወቀ ስፍራ እንደወሰዷቸው ገልጧል። ምንጭ_የአማራ ወጣቶች ማህበር በባህር ዳር
Source: Link to the Post