
ረቡዕ ሐምሌ 06/2014 ዓ.ም. ከሙስና ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉት የብሔራዊ አደጋ ስጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ የተጠረጠሩባቸውን ወንጀሎች ዝርዝር ፖሊስ ይፋ አድርጓል። ለበርካታ ዓመታት የብሔራዊ አደጋ ስጋትና ሥራ አመራርን በበላይነት የመሩት ኮሚሽነሩ ከኤልሻዳይ ሪሊፍ ኤንድ ዴቨሎፕመንት ከተባለው የበጎ አድራጎት ማኅበር ዳይሬክተር ጋር በመመሳጠር ፈጽመዋቸዋል የተባሉ ወንጀሎች ተጠቅሰውባቸዋል።
Source: Link to the Post