ሥራ አስፈፃሚው በቢሯቸው ተገደሉ

ሥራ አስፈፃሚው በቢሯቸው ተገደሉ

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አለባቸው አሞኜ በትላንትናው ዕለት በቢሯቸው ውስጥ መገደላቸው ተሰምቷል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው በቢሯቸው ውስጥ ባለጉዳዮችን ተቀብለው በሚያነጋግሩበት ወቅት ባለጉዳይ ሆኖ ወደ ቢሮአቸው በገባ ሰው በተፈጸመባቸው ጥቃት ህይወታአው ማለፉ ነው የተነገረው። ግድያውን የፈጸመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር እንደሆነና በቁጥጥር ስር መዋሉንና ምርመራ እያጣራ  እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

Source: Link to the Post

Leave a Reply