
ሩስያ ለወታደራዊ አገልግሎት የሚውል ሳተላይት አመጠቀች፡፡
ሩሲያ አዲስ ወታደራዊ ሳተላይት ወደ ጠፈር ማስወንጨፏ ተነግሯል።
የሩስያ መከላከያ ሚኒስትር የሃገሪቱ የስፔስ ማዕከል፣ወታደራዊ ሳተላይት ወደ ኦርቢት መላኩን አስታውቀዋል፡፡
“ሶዩዝ 2.1” የሚል ስያሜ የተሰጠውን ወታደራዊ ሳተላይት አርካንግልስክ ክልል ከሚገኘው ከፕሌሴስክ ወታደራዊ መንደር መወንጨፏን አር.ቲ ዘግቧል።
ሩሲያ ያስወነጨፈችው አዲሱ ወታደራዊ ሳተላይት ኦርቢት ላይ ደርሶ መሬት ላይ ካለ የመቆጣጠሪ ጣቢያ ጋር ግንኙት ማድረጉን እና በአግባቡ ስራ መጀመሩም ተነግሯል፡፡
ሳተላይቱን በሩሲያ ኤሮስፔስ ኃይል ውስጥ የጠፈር ተዋጊዎች ያስወነጨፉት ሲሆን፤ ተዋጊ ሃይሎቹ ሳተላይቱን ሶዩዝ 2.1 በተባለ ዘመናዊ ማስወንጨፊያ ተሸከርካሪ በመጠቀም የተሳካ ስራ መስራታቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
መጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን
Source: Link to the Post