ቅዱስ ሲኖዶስ በነነዌ ጾም የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ በጾመ ነነዌ የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን መግለጫ ሰጥቷል፤ በዚህም የምእመናን…

https://cdn4.telegram-cdn.org/file/uk6LoNwwpnBUMKND529gU2_YEIyhhxApQeUlAyEGH8Xt6k9gtOKEDDoxagoJxuU_ovwaN6Xv2acAllnOGuyhBdyYHMdJX2SR73yupOO8cApAqMBlUdBPkHJQka_-deqnijTe_9K3StegNEkGFuWPHcbAikcbA8_cwZYlmDoAu0Xu3RZ1g4bXcpfIxmgySaLYIXVbdUUU-f0S9HAGIVEhDQHL3aPlN8wKl9nMTzfSatMATRdcIGApPHuUnCZ3NQe6hJ6r5-efgsDmq_5v8pUJvrI9RLNrPEwzcKNNg6Kqft3jC43TjAtiT-3RSWXqHgw5t9lq-p6BKfCbMx-95sTo5g.jpg

ቅዱስ ሲኖዶስ በነነዌ ጾም የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ

በጾመ ነነዌ የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን መግለጫ ሰጥቷል፤ በዚህም የምእመናን ድርሻ ምን እንደሆነ ተገልጿል፡፡

ሁሉም ምእመናን እና ምእመናት በጾመ ነነዌ በሦስቱም ቀናት ጥቁር ልብስ መልበስ፣ በጸሎት መርሐ ግብሩ ተገኝቶ ጸሎት መጸለይ እና የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እና የአባቶችን መልእክት ሰምቶ መተግበር እንደሚገባው ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል፡፡

የጸሎት መርሐ ግብሩም ጠዋት ኪዳን እና ምሕላ፣ ቅዳሴ፣ የሰርክ የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብር እንዲሁም ማታ የቤተሰብ ጸሎት ናቸው፡፡

በመጨረሻም ምእመናን ለጸሎት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሚሄዱበት ጊዜ ለጸሎት ከሚያስፈልጉ መጽሐፍት ውጪ ሌላም ምንም ዓይነት መፈክር ይዞ መምጣት የማይቻል መሆኑን አስረድተዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን

Source: Link to the Post

Leave a Reply