ዛሬ ማክሰኞ ከጠዋቱ 1:50 በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አየርጤና ሞቢል አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ዉስጥ እድሜዉ 38 አመት የሆነ ሰዉ ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል ።
በሌላ በኩልም ዛሬ ከቀኑ 5:55 በአቃቂ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 አሳማ ግቢ አካባቢ በሚገኝ ወራጅ ወንዝ ውስጥ እድሜዉ 30 ዓመት ሰዉ ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል ።
የኮሚሽን መስሪያ ቤታችን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የሟቾቹን አስከሬን ከወንዝ ዉስጥ አዉጥተዉ ለፖሊስ አስረክበዋል ።
ስለግለሰቦቹ አሟሟት ፖሊስ እያጣራ በአዲስ አበባና ኦሮሚያ ልዩ ዞን በሀምሌ ወር በተለያዩ ምክንያቶች ወንዝ ዉስጥ ሞተዉ የተገኙ ሰዎች ቁጥር 9 ሆኖ ተመዝግቧል ሲል የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታዉቋል።
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/
onelovebroadcast
ዌብሳይት https://ethiofm107.com/
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
Source: Link to the Post