
በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ አካባቢ ታጣቂዎች በአርሶ አደሮች ላይ የሚፈጽሙት እገታ እና ግድያ እየተበራከተ መሄዱን የክልሉ ባለሥልጣናት መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። ሰኔ 17 ቀን 2015 ዓ.ም አሻራ ሚዲያ ፣ ባንድ ሳምንት ውስጥ በሁለት ቀበሌዎች ሦስት አርሶ አደሮች ተገድለው ሦስቱ እንደታገቱና በጸጥታ ችግር ሳቢያ የግብርና ሥራ መስተጓጎሉን ዘገባው ገልጧል። የጥቃቱ ፈጻሚዎች የክልሉ መንግሥት ምኅረት አድርጎላቸው የነበሩ፣ የቅማንት አማጺ ቡድን ታጣቂዎች እንደኾኑ ምንጮች ተናግረዋል ተብሏል። የዞኑ አስተዳደር በበኩሉ፣ አካባቢውን የሚያረጋጋ የጸጥታ ኃይል መሠማሩቱን እንደገለጸ ተጠቁሟል። ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:- // Youtube:- https://www.youtube.com/channel/UCPmgFzP2ZPmdGjHxXjigJaw // Ashara Tv – https://www.youtube.com/channel/UC2LZu_N0iOJipVUw3RyR4Ng // https://www.facebook.com/asharamedia24 // ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedia24
Source: Link to the Post