
ትላንት ሰኞ በሱዳን የአሜሪካ የዲፕሎማቶች አጃቢ መኪና ላይ ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊው አንቶኒ ብሊንከን ገለጹ።
ሆኖም ሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ብለዋል።
ለቡድን ሰባት ሀገራት ስብሰባ ጃፓን የሚገኙት ኃላፊው “ይህ ድርጊት ግዴለሽነት የተሞላበት፣ ኃላፊነት የጎደለውና በርግጥም ደህንቱ ያልተጠበቀ ነው” ብለዋል።
በሌላ በኩል በሱዳን የአውሮፓ ህብረት አምባሳደሩ ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በተቀናቃኝ ሃይሎች ውጊያ ውስጥ ባለችው ካርቱም በሚገኘው ቤታቸው ጥቃት ደርሶባቸዋል።
አየርላንዳዊው ዲፕሎማት አይደን ኦሃራ “የከፋ ጉዳት” እንዳልደረሰባቸው የሀገራቸው ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሚሼል ማርቲን አረጋግጠዋል።
ሚኒስትሩ ጥቃቱን ዲፕሎማቶችን የመጠበቅ ግዴታ እየተጣሰበት ነው ሲሉ ገልጸውታል።
በሱዳን ከሶስት ቀናት በፊት በተቀሰቀሰው ውጊያ 185 የሚጠጉ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ከ1 ሺህ 800 የሚልቁ ሰዎች ደግሞ ለጉዳት ተዳርገዋል።
ከተማዋ በአየር ጥቃትና በቀላል የቡድን መሳሪያዎች የተገዙ ውጊያዎችን እያስተናገደች ነው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ሚያዝያ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን
Source: Link to the Post