በሱዳን የአሜሪካ ተሽከርካሪ ላይ ተኩስ ሲከፈት የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ጥቃት ደረሰባቸውትላንት ሰኞ በሱዳን የአሜሪካ የዲፕሎማቶች አጃቢ መኪና ላይ ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር የአሜሪካ ውጪ…

https://cdn4.telegram-cdn.org/file/EjOYcycsqNOe4amZ5vbSYUDVnaR2SvdIpLJrz_D05fbJKy5PY4bCvRUeSFYEPsCSR4epxLxgNYl009wOXXrCphbAGB1T7g1hXkBXEX-W3mfMWp43FEMVXS5Q3XBn_Qo_gI0Ox1nIgr7oDlrlcKcxAR4dGua0GnCXsyC9VEOH8vOTspAOwdxnE_LsL1yvfBNgneu99NicwIv2uqMQONwL3-RfSe9uEw8DC6dYMCcfukleTwVQ2ozHNPyx-3bRdtfj2k5qbzSB8xz0EZJO4FIaUb2BEMR3DMoq3i9beO6J_1R0JiYhoJn_zXx57syENHc1KjAbulVa6yHAGZQkh5LQHg.jpg

በሱዳን የአሜሪካ ተሽከርካሪ ላይ ተኩስ ሲከፈት የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ጥቃት ደረሰባቸው

ትላንት ሰኞ በሱዳን የአሜሪካ የዲፕሎማቶች አጃቢ መኪና ላይ ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊው አንቶኒ ብሊንከን ገለጹ።

ሆኖም ሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ብለዋል።
ለቡድን ሰባት ሀገራት ስብሰባ ጃፓን የሚገኙት ኃላፊው “ይህ ድርጊት ግዴለሽነት የተሞላበት፣ ኃላፊነት የጎደለውና በርግጥም ደህንቱ ያልተጠበቀ ነው” ብለዋል።

በሌላ በኩል በሱዳን የአውሮፓ ህብረት አምባሳደሩ ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በተቀናቃኝ ሃይሎች ውጊያ ውስጥ ባለችው ካርቱም በሚገኘው ቤታቸው ጥቃት ደርሶባቸዋል።

አየርላንዳዊው ዲፕሎማት አይደን ኦሃራ “የከፋ ጉዳት” እንዳልደረሰባቸው የሀገራቸው ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሚሼል ማርቲን አረጋግጠዋል።
ሚኒስትሩ ጥቃቱን ዲፕሎማቶችን የመጠበቅ ግዴታ እየተጣሰበት ነው ሲሉ ገልጸውታል።

በሱዳን ከሶስት ቀናት በፊት በተቀሰቀሰው ውጊያ 185 የሚጠጉ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ከ1 ሺህ 800 የሚልቁ ሰዎች ደግሞ ለጉዳት ተዳርገዋል።

ከተማዋ በአየር ጥቃትና በቀላል የቡድን መሳሪያዎች የተገዙ ውጊያዎችን እያስተናገደች ነው።

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ሚያዝያ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን

Source: Link to the Post

Leave a Reply