በሽሮና በርበሬ ውስጥ አደንዛዥ ዕፅ ደብቆ ወደ ውጭ ሀገር ለመላክ የሞከረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋለው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው መርካቶ ጣና የገበያ ማዕከል አካባቢ በሚገኝ ፖስታ ቤት ውስጥ ነው።
ተጠርጣሪው ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ ዕፅ በሽሮና በርበሬ ውስጥ ደብቆ በካርቶንና በፌስታል በማሸግ ወደ እንግሊዝ ለንደን በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ለመላክ ሙከራ ሲያደርግ ነው የተያዘው፡፡
@የአዲስ አበባ ፖሊስ
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
መጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን