በቱርክ እና ሶሪያ የሟቾች ቁጥር ከ 8 ሺህ አልፏል፡፡ባሳለፍነው ሰኞ በደረሰዉ ርዕደ መሬት በቱርክ እና ሶሪያ የሟቾች ቁጥር ከ 8 ሺህ 7 መቶ በላይ ማለፉ ተገልጿል፡፡የቱርክ የአደጋ መከላከ…

https://cdn4.telegram-cdn.org/file/tTF3vRuB7G8EPeuwSbgbJXzRBk4OExV0gTq6FNBxA_Gn7OYcpwlXY5tVvPX5_FSNi6bgUbdngNJt3ifdSLzNaeMxkxv9xgiMDKLMuaNJIPdG3KvjbW2TfaU_p70ltnlQt7gxTuIWMwPv2qJ7D-9cLQYV3-ly4SFjBZ_P4Xl4g7G1-eeVk3-_uiJ_nuD5so7GVx_NzeiWF9dOsCxnTlUjlGhgpeCHlr4-hdlNB9DOEE-Qi4Dt3IYCW86u0lVjN6qK_-ykmxQQ1StKDj4-mdObDCWamSZm-NQH839mJz1s13YVYsWvQxRjoAJtOt5UxIq4xJlVutSz3Q8_5jVJjW_OtQ.jpg

በቱርክ እና ሶሪያ የሟቾች ቁጥር ከ 8 ሺህ አልፏል፡፡

ባሳለፍነው ሰኞ በደረሰዉ ርዕደ መሬት በቱርክ እና ሶሪያ የሟቾች ቁጥር ከ 8 ሺህ 7 መቶ በላይ ማለፉ ተገልጿል፡፡
የቱርክ የአደጋ መከላከል ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ በአገሪቱ የሟቾች ቁጥር ከ 6ሺህ በላይ ሆኗል፡፡

በሶሪያ ያለዉን የሟቾች ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ነገር ግን የአገሪቱ የመንግስት ሚዲያ እንዳስታወቀዉ የሟቾች ቁጥር ከ 2ሺህ 5መቶ በላይ መድረሱን ነዉ ያስታወቀዉ፡፡

በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች ላይ እስካሁን የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 1 ሺህ 2 መቶ ሀምሳ መድረሱን የሶሪያ የጤና ሚኒስቴር አስታዉቋል፡፡
በአሸባሪዎች ቁጥጥር ስር ባሉ ቦታዎች የሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከ1ሺህ 2 መቶ 80 በላይ መድረሱን ዘ ዋይት ሄልሜት የተባለ የበጎ ፈቃደኞች ቡድን ገልጿል፡፡

በእስከዳር ግርማ
የካቲት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

Source: Link to the Post

Leave a Reply