ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም የትግራይ ልዩ ኃይል በመከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዛ ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ መንግሥት ሕግ የማስከበር ያለውን ርምጃ መውሰድ ከጀመረ በኋላ የኢንተርኔትና የስልክ አገልግሎቶች በመቋረጡ በአብዛኛው የትግራይ አካባቢ ምን እየተከናወነ እንደሆነ ለማወቅ እድል አልነበረም። በሠራዊቱ ላይ ጥቃት በተፈጸመበት ጊዜ በክልሉ ልዩ ኃይል ተይዘው ለሳምንታት የቆዩ የሠራዊቱ አባላት ምን እንደተፈጠረና አስካሁን የቆዩበትን ሁኔታ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
Source: Link to the Post