የኢትዮጵያ መንግሥት ሠራዊት የትግራይ ክልል ዋና ከተማን መቀለ መቆጣጠሩ ከተገለጸ በኋላ ሲያካሂድ የነበረው ዘመቻ መጠናቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፈው ሐሙስ ሠራዊቱ የመጨረሻው ምዕራፍ ያሉትን “ሕግ የማስከበር ዘመቻ” እንዲያካሂድ ካዘዙ በኋላ ቅዳሜ ኅዳር 19/2013 ዓ.ም የክልሉን ዋና ከተማ የፌደራል ሠራዊቱ ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠሩን ተገልጿል።
Source: Link to the Post