በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ

በትግራይ የሚካሄደው ሕግ የማስከበር ሥራ በዋነኝነት ኢትዮጵያን በማተራመስ ላይ በተሠማሩ ሥርዓት አልበኞች፣ በተንኮልና በሤራ በተሞሉ የሕወሐት ቡድን አባላት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እና ሕገ ወጥ ወንጀለኞችን ለፍርድ ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት በድጋሜ ማረጋገጡን ጽ/ቤቱ ገልጿል፡፡

ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ በብሔር ወይም በሌላ ወገንተኝነት ላይ የተቃኘ ነው የሚለውን የተሳሳተ እሳቤ ጽ/ቤቱ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ጽ/ቤቱ አስታውቋል፡፡

*************************

ህዳር 09/2013

Source: Link to the Post

Leave a Reply