በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ጎፋ ገብርኤል ጀርባ የተነሳዉ እሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዉሏል።
ዛሬ የካቲት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 9:20 ሰዓት ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ወረዳ 6 ጎፋ ገብርኤል ቤተክርስታያን ጀርባ ያገለገሉ አሮጌ ጎማዎች ላይ የተነሳዉ የእሳት ቃጠሎ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ዉሏል።
የእሳት አደጋዉ ከጎፋገብርኤል ቤተክርስቲያን ጀርባ በሚገኝ ጋራዥ አጠገብ ባለ ክፍት ቦታ የተከማቸ አሮጌ ጎማ ላይ ከደረሰዉ ጉዳት ዉጪ በቤተ ክርስቲያኑ ላይም ሆነ በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አልደረሰም ተብሏል።
በየውልሰው ገዝሙ
የካቲት 06 ቀን 2015 ዓ.ም