በአዲስ አበባ ትላንት ማምሻዉን በደረሱ ሦስት የእሳት አደጋዎች በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ደረሰ።

በአዲስ አበባ ትላንት ማምሻዉን በደረሱ ሦስት የእሳት አደጋዎች በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የእሳት አደጋና ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

በዚህም ትላንት ማምሻዉን 11:26 በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አደይ አበባ አካባቢ በአጋጠመ የእሳት አደጋ በኹለት ሆቴሎችና በአንድ ፔንሲዮን ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።

ኹለተኛዉ አደጋ ያጋጠመዉ ምሽት 12:20 ሰዓት ንፋሰ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ሲሆን፤ በአንድ ባጃጅ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ባጃጇ ሙሉ በሙሉ መቃጠሏ ተገልጿል።

በተጨማሪም ሦስተኛዉ አደጋ ያጋጠመዉ ምሽት 3:05 ሰዓት ላይ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ዘነበ ወርቅ ባጃጅ ተራ ሲሆን፤ በአጋጠመው የእሳት አደጋ የተለያዩ የንግድ አገልግሎት የሚሰጥባቸዉ 6 የንግድ ቤቶች ተቃጥለዋል።

ሦስቱንም የእሳት አደጋዎች ለመቆጣጠር አምስት ሰዓት የፈጀ ሲሆን፤ በደረሱት የእሳት አደጋዎች በሰዉ ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩም ተገልጿል።

Facebooktwitterredditpinterestlinkedinmail

Source: Link to the Post

Leave a Reply