በአዲስ አበባ ከተማ 6ኛ ዙር የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ስራ ትላንት ተጀምሯል።በ6ኛ ዙር በተመረጡ በሰባት ክፍለ ከተሞች ከግንቦት 03/09/2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉ ተከታታይ አምስት ወራት 50…

https://cdn4.telegram-cdn.org/file/OP6MVxG1aZ-USGF7FSl_ORYCaPipCDpPAUxvTFfxSy47IVUp2NtW-Ipamw-mkQnED37xaJ0-cY_9JszszWKHneeckk6ptOMmipiEX3MHjDGv3CEiP-XCX4akqA72NUb_zmTAurqz8rV4cCVeMLXO4NfIVDjJ9ZExk5sOadRvok-Sr5TZOZ7OvreMiwiYOVujnwvyUNXaJ11xZvCxeOv22obtq5Fh_W-v7R7jjuSDmxeuyJyARZ7hTojD7KjgZZCW1eVNgmd3EwFSWfV7WMEo4UEVFhwXlTfq7A7oZnRjkP-wfdgLGHcyOLcrw_Tl1ne6ou_8LCS5XGZI7MrAV2xQ3g.jpg

በአዲስ አበባ ከተማ 6ኛ ዙር የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ስራ ትላንት ተጀምሯል።

በ6ኛ ዙር በተመረጡ በሰባት ክፍለ ከተሞች ከግንቦት 03/09/2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉ ተከታታይ አምስት ወራት 50 ሺህ የመሬት ይዞታዎችን የማረጋገጥ ስራ ይካሄዳል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታውቋል።

ኤጀንሲው ምዝገባው ፦

👉 በኮልፌ ቀራኒዮ፣
👉 በቂርቆስ፣
👉 በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
👉 በቦሌ፣
👉 በአዲስ ከተማ፣
👉 በልደታና በአራዳ ክፍለ ከተሞች ባሉ 50 ቀጠናዎችና 211 ሰፈሮች እንደሚከናወን ገልጿል።

ይህ የይዞታ ማረጋገጥ እወጃ ከተላለፈ ከ15 ቀናት በኃላ የይዞታ ይረጋገጥልኝ ጥያቄዎች በክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤቶች ቀርበው ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ ይቻላል ተብሏል።

ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ በተመረጡ ቀጠናዎችና ሰፈሮች ስራው ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ባለቱ አምስት ወራት ውስጥ የመረጃ ልዩነት እንዳይፈጠር ሲባል ምንም ዓይነት የስመ- ንብረት ዝውውር አገልግሎት እንደማይሰጥ ኤጀንሲው ማስታወቅን ከአ/አ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ኢትዮጵያዊያን

ግንቦት 04 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

Source: Link to the Post

Leave a Reply