
የተሽከርካሪ እና አሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን እንዳስታወቀው በህጋዊ መንገድ ከምርመራ ተቋማት ቦሎ የሚወስዱ ተሽከርካሪዎች 48 ከመቶ ብቻ ናቸው ብሏል፡፡
ባለፉት ዘጠኝ ወራቶች በህጋዊ መንገድ ከምርመራ ተቋማት ፍቃድ አግኝተው ቦሎ የወሰዱ ተሽከርካሪዎች 330ሺህ ብቻ ናቸው ተብሏል፡፡
የአሽከርካሪ እና ተሸከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍሬው ደምሴ እንደተናገሩት፣ አሁን ላይ በአዲስ አበባ ደረጃ 650ሺህ ተሸከርካሪዎች እንደተመዘገቡ ገልጸው በየአመቱ ቦሎ የሚወስዱ ተሽከርካሪዎች ግን 450ሺህ የሚሆኑት ብቻ ናቸው ብለዋል፡፡
የተቀሩት ተሽከርካሪዎች አመታዊ ተሽከርካሪ ምርመራ የት እየሄዱ እንደሚያደርጉና ቦሎም ከየት እንደሚወስዱ አይታወቅም ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ ደረጃ እውቅና ተሰጥቷቸው ተሽከርካሪ ምርመራ የሚያደርጉ ከ50 በላይ የምርመራ ተቋት እንዳሉ የተነገረ ሲሆን፣አብዛኛዎቹ የአቅም ክፍተት እንዳለባቸው ተጠቅሟል፡፡
የአሽከርካሪ እና ተሸከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን እነዚህ ችግሮም ለመቅረፍ ከምርመራ ተቋማቱ ጋር በመቀናጀት አዲስ አሰራር መዘርጋቱንም ነው የገለጸው፡፡
በዚህም ተሽከርካሪዎች አመታዊ የቴክኒክ ምርመራ በቴክኖሎጂ በታገዘ የምረመራ አገልግሎት የሚሰጣቸው ይሆናልም ተብሏል፡፡
በሄኖክ ወ/ ገብርኤል
መጋቢት 27 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን
Source: Link to the Post