‹‹በአገልግሎት ወቅት ለተፈጠሩ ቅሬታዎች ይቅርታ እንጠይቃለን›› – ም/ከንቲባ አዳነች አበቤ

‹‹በአገልግሎት ወቅት ለተፈጠሩ ቅሬታዎች ይቅርታ እንጠይቃለን››… ምክትል ከንቲባ አዳነች አበቤ

በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ያሰናዳው የጳጉሜን አንድ ‹‹ የይቅርታ ቀን›› እየተከበረ ይገኛል፡፡

በዚህ ወቅት መልእክታቸውን ያስተላለፉት ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ የጳጉሜን ወር በትርጓሜው የምህረት ወር ተብሎ እንደሚታወቅ አስታውሰው ዛሬ ላይ ስለ ቅርታና ምህረት ማውራት ተገቢ መሆኑን አንስተዋል፡

ይቅርታ የትላንትን ስህተት፤ በበደልና ቁርሾ በመተው ዛሬን በጥበብ ለመኖር የሚያስችለን መንገድ አንደመሆኑ በአዲስ አበባ ከተማ የአገልግሎት ወቅት ለተፈጠሩ ቅሬታዎች የከተማዋን ነዋሪዎች ይቅርታ እንደሚጠይቁ ገልጸዋል፡፡

‹‹አዲስ አበባን እንደስሟ ውብና ማራኪ ለማድረግና የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ለመጨረስ የነዋሪዎቿን ድጋፍ እንፈልጋለን፤ ያለ ከተማዋ ነዋሪ አጋርነት ምንም መስራት አይቻልም›› በማለት ነው ያስረዱት፡፡

የታሪክ ምሁራን የቆየውን የኢትዮጵያውያንን የይቅርታ ባህል መልሰው እንዲያስተምሩ፣ ፖሊተከኞችም ከቂምና ጥላቻ ይልቅ ይቅርታን፤ አብሮነትንና አንድነትን እንዲሰብኩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በበዓሉ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ፣ የሀይማኖት መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ወርሀ መስከረምን በአዲስ ተስፋ ለመቀበልና ለፈጣሪ የምናቀርበው ልመና እንዲሰማ በይቅርታ የታደሰ ልብ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በበቀል የሰለለን አጥንት የሚያለመልመው ይቅርታ በኢትዮጵያውን ዘንድ በግጥም፤በንግግር፣ በጫወታ በሃል እንደሚነሳና የየእለት ሕይወት አካል መሆኑን ጠቅሰው የይቅርታ አድራጊ ልብ ለሌሎች ይተርፋል ነው ያሉት፡፡

አዲሱን አመት ከበቀልና ጥላቻ ስሜት ርቀን በተስፋ በመቀበል ኮቪድን የምናሸንፍበት እንዲሆን እመኛለው በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Source: Link to the Post

Leave a Reply