You are currently viewing በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር በአሜሪካ ሎዛንጅለስ እና ካሊፎርኒያ ከተማ ከሚኖሩ የኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር እንደሚወያዩ የአሜሪካ ው…

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር በአሜሪካ ሎዛንጅለስ እና ካሊፎርኒያ ከተማ ከሚኖሩ የኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር እንደሚወያዩ የአሜሪካ ው…

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር በአሜሪካ ሎዛንጅለስ እና ካሊፎርኒያ ከተማ ከሚኖሩ የኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር እንደሚወያዩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ግንቦት 3/2015 ዓ.ም አሻራ ሚዲያ አምባሳደር ሐመር፣ ከትናንት ጀምሮ እስከ ግንቦት 12 በከተማዋ በሚኖራቸው ቆይታ፣ ከአማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬይና ሱማሊያ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች እና ባጠቃላይ ከኢትዮዊያን አሜሪካዊያን ጋር እንደሚወያዩ መስሪያ ቤቱ ገልጧል። የአምባሳደር ሐመርና የኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያኑ ውይይት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት መካከል ፕሪቶሪያ ላይ በተደረሰው ሰላም ስምምነት አፈጻጸ፣ በሌሎች የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች እንዲኹም የኢትዮጵያዊያን ሴቶችን አቅም በመገንባት ዙሪያ ያተኮረ እንደሚኾን መረጃው አመልክቷል። ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:- // Youtube:- https://www.youtube.com/channel/UCPmgFzP2ZPmdGjHxXjigJaw // Facebook:- https://www.facebook.com/asharamedia24 // ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedia24

Source: Link to the Post

Leave a Reply