
በኢትዮጵያ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ከገደል አፋፍ ላይ ይገኛል ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ገለጸ፡፡
ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተቋርቋሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የአለም የሰብዓዊ መብቶች አያያዝን አስመልክቶ በ412 ገፆች የተቀነበበ ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም በኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በከፍተኛ ሁኔታ መሸርሸሩን ጠቅሶ፣ በትግራይ፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከ29 ያላነሱ ጋዜጠኞችን እና የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ታስረው እንደሚገኙ አስታውሷል፡፡
ሪፖርቱ በመጋቢት ወር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ምርመራ ለማካሄድ እና ግድያውን የፈፀሙትን ለፍርድ ለማቅረብ ቃል የገባ ቢሆንም፣ በአመቱ መጨረሻ ድረስ ስለ ምርመራ እና የክስ ሂደቶች ምንም አይነት መረጃ ይፋ አለመደረጉን አክሏል፡፡
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
መጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም
ለተጨማሪ መረጃዎች የቴሌግራምና የዩቲዩብ ቻናሎቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/@onelovebroadcast
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን
Source: Link to the Post