
በኢትዮጵያ በተጨባጭ እየተባባሱ የሚሄዱ የደኅንነት ስጋቶች እና የመብት ጥሰቶች መቀጠላቸውን የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች የባለሙያዎች ቡድን ባወጣው አዲስ ሪፖርት አመለከተ። በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ሁኔታ የመረመረው በተባበሩት መንግሥታት ድርጀት የሚደገፈው የመብቶች ኮሚሽን አዲስ ባወጣው ሪፖርት፤ በተለይ በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በአፋር ክልሎች ያለው ሁኔታ እንዳሰሰበው አመልክቷል።
Source: Link to the Post