
ከሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ እና ከአማራ ክልል አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ መንገደኞች ሙከ ጡሪ ከተማ ላይ በፀጥታ ሃይሎች መታሰራቸዉን ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቷል፡፡
መንገደኞቹ ለጣቢያችን እንደተናገሩት “ ወደ አዲስ አበባ አትገቡም በሚል የአካባቢዉ የፀጥታ አካላት ከመኪና በማስወረድ ለእስርና እንግልት ዳርገዉናል” ብለዋል፡፡
ከአማራ ክልል መርሃቤቴና ጃማ ተነስተዉ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ የነበሩ መንገደኞችንም ወደ ለሚ ከተማ እንዲመለሱ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የፀጥታ ሃይሎቹ አዲስ አበባ እንዳይገቡ መንገደኞቹን የከለከሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በጠራችዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ለመሳተፍ አስባችኋል በሚል እንደሆነም ታዉቋል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
የካቲት 01 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
Source: Link to the Post