
የአስራ ሁለተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከል ለከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሚያበቃ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር ዝቅተኛ በመሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አሠራር ሊከተል መሆኑ ተነገረ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ የ2014 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤትን በማስመልከት አዲስ አበባ ውስጥ በሰጡት መግለጫ ላይ ለፈተናው ከተቀመጡት አጠቃላይ ተማሪዎች መካከል ከግማሽ በላይ ውጤት ያስመዘገቡት ከአራት በመቶ በታች እንደሆኑ አስታውቀዋል።
Source: Link to the Post