በደቡብ አፍሪካ ሁለት ተሽከርካሪዎች ተጋጭተው 20 ሰዎች ሞቱ

https://gdb.voanews.com/03370000-0aff-0242-8888-08daf113a194_w800_h450.jpg

ሊምፖፖ በተሰኘው የደቡብ አፍሪካ አውራጃ በትናንትናው ዕለት አንድ የሰዎች ማጓጓዣ አውቶብስ ከገንዘብ አመላላሽ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ 20 ሰዎች ወዲያውኑ ሲሞቱ 60 የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ገንዘብ አመላላሹ ተሽከርካሪ መንገዱን ሲስት ከአውቶብሱ ጋር ፊት ለፊት በመላተሙ አደጋው ሊደርስ መቻሉን የአካባቢው የትራንስፖርት መምሪያ አስታውቋል።

ከተጎጂዎቹ መካከል አስር የሚሆኑት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው በመሆኑ ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆን ሌሎች ሰዎች በአካባቢው ባለ ወንዝ ሰምጠው እንደሁ ለማጣራት የፖሊስ ባህር ጠላቂዎች ወንዙን እያሰሱ ናቸው።

የአደጋው መንስኤ አሁንም በመጣራት ላይ ሲሆን ሰሞኑን የሚጥለው ከፍተኛ ዝናብ አካባቢውን እያጥለቀለቀ መሆኑን ባለሥልጣናት ለኤ.ኤፍ.ፒ የዜና ወኪል ተናግረዋል።

Source: Link to the Post

Leave a Reply