በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንዳስታወቀው በአጊቱ ጉደታ ድንገተኛ ሞት ማዘኑን ገልጿል።
ኤምባሲው የግድያ ሁኔታው በቶሎ ተጣርቶ እንዲገለፅና ወንጀለኛ ተለይቶ ለፍትህ እንዲቀርብ ከጣሊያን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑንም ገልጿል።
አጊቱ ጉደታ በጣሊያን ገጠራማ ስፍራ መሬት ገዝታ ፍየል እያረባች፤ አይብ በማምረት ትተዳደር እንደነበረ ሪፐብሊካ የተባለ የጣልያንኛ ጋዜጣ በሰራው ዘገባ አስፍሯል።
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ስርጭቶችን፣ዜናዎችን እና ሌሎች ዝግጅቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/ethiofm107dot8 ይቀላቀሉ።
ድረ ገጻችንን https://ethiofm107.com/ ይጎብኙ::
ታህሳስ 21 ቀን 2013 ዓ.ም
Source: Link to the Post