በጦርነቱ 3.2 ቢሊዮን ብር የሚገመት የውሀ መሰረተልማት መውደሙ ተገለፀ

https://gdb.voanews.com/09320000-0a00-0242-7e4f-08db064a0731_tv_w800_h450.jpg

በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት 3.2 ቢሊዮን ብር የሚገመት የውሀ መሰረተልማት መውደሙን የውሀ እና ኤነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለፁ፡፡

ከትግራይ እና ከአማራ ክልሎች ያነጋገርናቸው ነዋሪዎችም የውሀ ተቋማቱ በጦርነቱ በመውደማቸው ችግር መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

ተቋማቱን ለመጠገን የአጭር እና የረዥም ጊዜ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑን ዶ/ር ሀብታሙ ገልፀዋል፡፡

አስተዳደራዊ መዋቅር ባለባቸው የአፋርና የአማራ ክልሎች ከውሀ ቢሮዎች ጋራ እየተሠራ እንደሆነ የተናገሩት ዶ/ር ሀብታሙ፣ በትግራይ ክልል ግን መዋቅሩ ስለሌለ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከማዕከል ባለሞያዎችን እየላከ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ዘገባ ያገኛሉ።

Source: Link to the Post

Leave a Reply