ብሩንዲ በፖሊዮ ምክንይት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች

https://gdb.voanews.com/36abcae3-b4d7-45f9-9147-ee2fc12962f4_w800_h450.jpg

በብሩንዲ አንድ የአራት አመት ህጻን እና ከልጁ ጋር ግንኙነት የነበራቸው ሌሎች ሁለት ህፃናት ላይ የፖሊዮ በሽታ ከተገኘ በኃላ፣ የሀገሪቱ መንግስት ብሄራዊ የህዝብ ጤና አስቸኳይ አዋጅ አውጇል። 

የፖሊዮ ወረርሽኝ በብሩንዲ ሲከሰት ከ30 አመት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። 

ከህፃናቱ በተጨማሪ የጤና ባለስልጣናት አምስት የፖሊዮ ናሙናዎችን በቆሻሻ ውሃ ላይ በማግኘታቸው ሁለተኛው አይነት የፖሊዮ ቫይረስ እየተዘዋወረ መሆኑን አረጋግጠዋል። በከፍተኛ ሁኔታ ተላላፊ የሆነው ይህ በሽታ በተበከለ ውሃ እና ምግብ ወይም በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር በሚኖር ግንኙነት ይተላለፋል።

የሀገሪቱ መንግስት አዲስ ከተወለዱ ህፃናት ጀምሮ እስከ ሰባት አመት ላሉ ህፃናት የሚሰጥ የክትባት ዘመቻ እያዘጋጀ ሲሆን በሳምንታት ጊዜ ውስጥ መሰጠት እንደሚጀምር ተገልጿል። 

Source: Link to the Post

Leave a Reply