ብራዚል ሉላ ዳሲልቫን ለሶስተኛ ጊዜ የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት አድርጋ ሾመች፡፡
ብራዚል ከሳምንታት በፊት ባካሄደችው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሉላ ዳ ሲልቫ ማሸነፋቸውን ማሳወቋ ይታወሳል፡፡
ይሁን እንጂ ቦልሶናሮ እና ደጋፊዎቻቸው የምርጫው ውጤት ላይ ቅሬታ ሲያሰሙ መቆየታቸውም አይዘነጋም፡፡
ዛሬ ዳሲልቫ ለብራዚል ለሶስተኛ ጊዜ ፕሬዝደንት የሚያደርጋቸውን ቃለ-ማሃላ ፈፀመዋል፡፡
ከሰሞኑ ፔሌን ያጣችው ብራዚል የሶስት ቀናት ብሄራዊ ሀዘን ማወጇ የሚታወስ ቢሆንም የሉላ ዳሲልቫ በዓለ ሲመት በደመቀ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡
የአንጋፋው የእግር ኳስ ጭበበኛ ፔሌ የቀብር ስርዓቱ ላይ ዳሲልቫ እንደሚገኙም ይጠበቃል፡፡
በአብዱሰላም አንሳር
ታህሳስ 24 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/
onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።