ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ብራዚል በዜጎቿ ላይ የወፍ ጉንፋን ምልክት መታየቱን ተከትሎ ለ6 ወር የሚቆይ የጤና አስቸኳይ አዋጅ ጥላለች፡፡
በሀገሪቱ አቪያን የተሰኘ የወፍ ጉንፋን በ 7 ዜጎች ላይ መከሰቱ ተሰምቷል፡፡
የዚህን የወፍ ጉንፋን ስርጭት ለመግታት ይረዳ ዘንድ ለ6 ወራት የሚቆይ አስቸኳይ አዋጅ መጣሉን የሀገሪቱ መንግስት አስታወቋል፡፡
ምልክቶቹ እስካሁን በኢስፕሪቶ ሳንቴና እና በሪዮ ዴጄኔሮ እንደታዩ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ብራዚል ከአለማችን ከፍተኛ የሆነ የዶሮ ስጋ ወደ ዉጭ የምትልክ ሀገር ነች፡፡
በአመት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጣ የዶሮ ስጋን ለተለያዩ ሀገራት ትሸጣለች፡፡
አባቱ መረቀ
ግንቦት 15 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
Source: Link to the Post