የቀድሞ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ስዩም መስፍንን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የህወሓት አመራሮች መገደላቸውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አስታወቀ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና አምባሳደር የነበሩት አቶ ስዩም መስፍን፣ በተለያዩ የሥልጣን ቦታ ላይ የነበሩት አቶ አባይ ጸሐዬ፣ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ እንዲሁም ከመከላከያ ሠራዊቱ ከድተዋል የተባሉት ኮሎኔል ኪሮስ ሐጎስ መገደላቸው ተነግሯል።
Source: Link to the Post