አጥፍቶ ጠፊ ፓኪስታን ውስጥ ወደ ሃምሣ ሰው ገደለ

https://gdb.voanews.com/09320000-0a00-0242-4eb7-08db02da76fd_w800_h450.jpg

ፓኪስታን ውስጥ በሰሜን የአገሪቱ ክፍል በምዕመናን በተሞላ አንድ መስጊድ ውስጥ ዛሬ ከሰዓት በኋላ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ ፀሎት ላይ የነበሩ ቢያንስ 47 ሰዎች ተገደሉ።

የኺበር ፓኽቱንዃ ክፍለ ግዛት ዋና ከተማ በሆነችው ማዕከላዊቱ ፔሻዋር በአጥፍቶ ጠፊ መፈፀሙ በተነገረው በዚህ ጥቃት ከተገደሉት ሌላ 140 የሚሆኑ መቁሰላቸው ተነግሯል።

የአገሪቱ የፀጥታና ደህንነት ምክትል ኮሚሽነር ሻፊኡላ ኻን ከፍርስራሽ ውስጥ ሁለት ሰው በህይወት ማውጣታቸውን ማምሻውን ተናግረዋል።

በጥቃቱ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል አብዛኞቹ የክፍለ ግዛቲቱ ፖሊሶች መሆናቸው ተመልክቷል።

አደጋው የደረሰበት መስጊድ በደህንነትና የመንግሥት ባለሥልጣናት የሚዘወትር መሆኑም ተነግሯል።

Source: Link to the Post

Leave a Reply