ዉድ ወንድሞቼና እህቶቼ!
አባሪ የተደረገላችሁ መልእክት ከእግዚአብሔር እዉነተኛ አገልጋይና መልእክተኛ እንዲሁም የተዋሕዶ ሃይማኖት አርበኛ የሆኑ አባት፤ ለኢትዮጵያ መንግሥት፣ ለተዋሕዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት መሪዎች እንዲሁም ለዓለም መንግሥታት የተጻፈ ደብዳቤ የያዘ ነዉ፡፡ በመልእክቱም አሁን ያለዉ የዐብይ መንግሥት ከነመዋቅሩ እና እግዚአብሔር ከሚያዉቃቸዉ በጣት ከሚቆጠሩ እዉነተኛ አገልጋዮች ዉጭ ያሉት የኦርቶዶክስ ተዋሕህዶ ሃይማኖት መረዎች በተለያየ መዋቅር ያሉ መሰናበታቸዉን የሚገልጽና፤ ከእንግዲህ ሦስተኛ ኢሕአዴግ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ባለጊዜ እንደማይሆን፤ ከእግዚአብሔር መደምደሚያ ቁጣና ጠረጋ በኋላ የእግዚአብሔር ብርሃናዊ መንግሥት በኢትዮጵያ ተግባራዊ እንደሚሆን የሚገልጽ ነዉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ስለ ዓመፃቸዉና ቀለዉ በመገኘታቸዉ ምክንያት የመጀመሪያዉ የእግዚአብሔር ቁጣና ቅጣት የሚያርፍባቸዉ ግለሰቦችና ድርጅቶች እንዲሁም ተቋማት ማንነታቸዉ የተገለጸበት፤ እንዲሁም ሌሎች ጉዳዮችንም የያዘ ስለሆነ በትእግሥትና በማስተዋል እስከመጨረሻዉ እንድታነቡት በትህትና አሳስባለሁ፡፡
የእናንተዉ ወንድምና አገልጋይ