ባሕር ዳር: መስከረም 11/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በ1868 በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት ተዘርፈው የተወሰዱ የኢትዮጵያ ቅርሶች በለንደን ለኢትዮጵያ ኤምባሲ ተመልሰዋል፡፡ ከተመለሱት ቅርሶች መካከል በ1868 ከመቅደላ የተዘረፈ የመድኃኒዓለም ታቦት፣ የልኡል አለማየሁ የጸጉር ዘለላ፣ ከብር የተሰሩና በነሃስ የተለበጡ ሶስት ዋንጫዎች እንዲሁም በዘመኑ ጦርነት ላይ የዋለ የጦር ጋሻ ይገኙበታል፡፡ የቅርሶቹ ርክክብ ሥነ ሥርዓት የተካሄደው ለንደን በሚገኘው ዝነኛው የአቴናየም ክለብ […]
Source: Link to the Post