ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ፥መግለጫውን የሠጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ…

https://cdn4.telegram-cdn.org/file/Z7wvl4OPuO52P9uGENfh1E5QAZNik4mNCknqtRQPLI7wyVtC8maA3u-4qUOHGCRTm9-QA8EPvDgG6rGUYLLP5YdJTo4ZF9168c-CnmCjqpi4cf_qcybuz5njfga5Pzry690neuHMscw6j3tMezt4ao4SyuhYEbMb2lzIZTpZFbdAxFhnVKxIgTyXFx_heGzBQsblW7-qV-lMmDin0_KsYpw063slsLe1kJCX2BWdE2onXkYViz72mZZZBhdwLICI148nz6Dt_vF9TokZVkflcA3akOo2mEdnUDX5_LNgBbQEYtlOjIZKzqNYQQLwY9fD6OJBEPu0u7zJPGDEl1CB3Q.jpg

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ፥

መግለጫውን የሠጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እና ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ : በመንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው።

ቅዱስነታቸው ዛሬ ማለዳ በተሰማው ሕገ ወጥ “ሢመተ ጳጳሳት” ጉዳይ በሰጡት መግለጫ ጉዳዩ ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጪ በሕገወጥነት የተከናወነ መሆኑን በመግለጽ :-

1. በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት በአስቸኳይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።

2. መንግሥት ክስተቱ በሀገር ላይ ጭምር የሚያስከትለውን ጉዳት ተመልክቶ በጉዳዩ ላይ ሕጋዊ ሓላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

3. ምዕመናን ቤተክርስቲያንን ከመቸውም ጊዜ በላይ በንቃት በሀሣብና በጸሎት እንዲጠብቁ ቅዱስነታቸው ጥሪ አቅርበዋል።

Source: Link to the Post

Leave a Reply