ክቡር ኮሌጅ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሚገቡ ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረውን የህይወት ክህሎትና ቴክኖሎጂ ስልጠና አጠናቆ አስመረቀ፡፡
ተማሪዎች የክረምት የእረፍት ጊዜያቸውን በመጠቀም በቀጣይ ለሚጠብቃቸው ትምህርት ቅድመ-ዝግጅት የሚያበቃቸውንና ለጠቀላላ እውቀት የሚሆን ትምህርት መቅሰም እንደቻሉ ተገልጿል፡፡
ኮሌጁ ትምህርቱን የሰጠው በነጻ ሲሆን በዚህ ለሶስተኛ ዙር በተሰጠው በዚህ የክረምት የትምህርት እድል 800 የሚሆኑ ተማሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸው ታውቋል፡፡
የኮሌጁ ዲን ደሳለኝ መኩሪያ ተማሪዎች በኢሞሽናል ኢንተለጀንስ፣በፕሮግራሚንግ፣በዌብ ዴቨሎፕመንት፣ በሥራ ፈጠራ፣ በአመራር ክህሎት፣ግራፊክስ ዲዛይን፣ እንዲሁም በዌብ ዴቨሎፕንት ትምህርቶች ላይ በቂ እውቀት እንዲያገኙ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
በኮሌጁ ሥልጠና ወስደው ያጠናቀቁ ተማሪዎችም፤ ከ150 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 800 ተማሪዎች መሆናቸውም ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube
https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/video