
ባለፉት ዓመታት በኮሜዲ ሥራዎቹ፣ በቴሌቪዥን እና በዩቲብ ፕሮግራሞቹ እውቅናን ያገኘው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ፣ ለበጎ አድራጎት እና ለእምነት ተቋማት ድጋፍ ባደረጋቸው የገቢ ማሰባሰቢያ ሥራዎቹ ከፍተኛ አድናቆትን አግኝቷል። በተለይ ከዚህ ቀደም ባልታየ ሁኔታ በቅርቡ ለሜቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል 3 ሚሊዮን ዶላር ማሰባሰብ ችሏል። እሸቱ ስለ ሥራው አሁን ስለደረሰበት የስኬት ጉዞው ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርጓል።
Source: Link to the Post