
ዊጋን አትሌቲክ የቀድሞውን የአርሰናል እና ማንቸስተር ሲቲ ተከላካይ አዲሱ አሰልጣኙ አድርጎ ሾሟል ፡፡
የኮሎ ቱሬ ኮንትራት ለሶስት ዓመት ከስድስት ወር የሚዘልቅ እንደሆነም ተነግሯል ፡፡
የ41 ዓመቱ አይቮሪኮስታዊ ኃላፊነቱን የተረከበው ሊያም ሪቻርድሰንን ተክቶ ነው ፡፡ የሻምፒየንሺፑ ክለብ የቀድሞውን አሰልጣኝ ያሰናበተው በዚህ ወር መጀመሪያ እንነበር ይታወሳል ፡፡
ቱሬ ያለፉትን አምስት ዓመታት በብሬንዳን ሮጀርስ ስር በሴልቲክ እና ሌስተር ሲቲ ሰርቷል፡፡ በኃላፊነት የሚረከበው የመጀመሪያ ስራውም ሆኗል ፡፡
ዊጋን በታህሳስ መጀመሪያ ከሜዳው ውጪ ሚልዎልን ሲገጥም ቱሬ በዋና አሰልጣኝነት የመጀመሪያ ጨዋታውን ይመራል፡፡
በአቤል ጀቤሳ
ህዳር 20 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
Source: Link to the Post