
ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች የህዝበ ውሳኔ ድምፅ እየሰጡ ሲሆን በአንድ የምርጫ ጣቢያ ሂደቱ ተቋርጧል ተብሏል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀው በወላይታ ዞን ስር በሌ የምርጫ ማዕከል ‘ሶርቶ’ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው ሶርቶ 1 ምርጫ ጣቢያ ውስጥ የህግ ጥሰት መፈፀሙን አረጋግጫለሁ ብሏል።
በምርጫ ጣቢያው ድምፅ በመስጠት ሂደት ወቅት የቀበሌ አስተዳደር ሀላፊዎች በሶርቶ 1 ምርጫ ጣቢያ በመገኘት 105 የሚሆን የግለሰብ ጊዜያዊ መታወቂያዎችን ድምፅ ለመስጠት ለተሰለፋ ዜጎች በማደል ህገ ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው ተገኝተዋል።
በዚህም የህግ ጥሰቱ እስከሚጣራ ድረስ ሶርቶ 1 ምርጫ ጣቢያ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱን እንዲያቋርጥ መወሰኑ ታውቋል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
Source: Link to the Post