የሃይማኖት አባቶች ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በመልዕክታቸውም÷ የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የፍቅር እና የትህትና መሠረት በመሆኑ ክርስቲያን ምዕመኑ ርስበርስ በመፋቀር እና በመዋደድ በተግባር ሊተረጉመው ይገባል ሲሉ የሃይማኖት አባቶች አሳስበዋል፡፡
እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ወደዚች ምድር መምጣቱ ለሰው ልጅ ያለውን ፍቅር ማሳያ በመሆኑ እኛም እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያሳየውን ፍቅር ማሳየት ይገባናል ብለዋል።
ርስበርስ መዋደድ በሰላምና በፍቅር መኖር አምላካዊ ትእዛዝ ነውና በመንፈሳዊና አለማዊ የስራ ሃላፊነት የምንገኝ ሰዎች የእግዚአብሔር ትእዛዙን ማክበር ግዴታችን ነው ብለዋል።
በዓሉ የትህትና እና የፍቅር በዓል እንደመሆኑ ክርስቲያን ምዕመኑ በተለያየ ምክንያት የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብ እና ካለው በማካፈል በዓሉን አብሮ ማሳለፍ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ታህሳስ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/…/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።