በደቡብ ክልል ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ህዝበ ውሳኔ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡
ሕዝበ-ውሳኔውንም በተሳካ መልኩ ለማከናወን በቂ ዝግጅት መደረጉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።
የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ÷በደቡብ ክልል ሥር የሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ለሚካሄደው ሕዝበ-ውሳኔ ስኬታማ ክንውን በቦርዱ በኩል በቂ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
በምርጫ ሂደት የሚያጋጥሙ ጉድለቶች የሚሻሻሉበት እና አፋጣኝ እርማት የሚወሰድበት የአሰራር ሥርዓት መዘርጋቱንም ጨምረው ገልጸዋል።
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ሥር የሚገኙና ህዝበ-ውሳኔ የሚካሄድባቸው ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ደራሼ) ናቸው፡፡
የሕዝበ- ውሳኔው የድምፅ አሰጣጥ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚከናወን ታውቋል፡፡
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም
Source: Link to the Post