የመገጣጠሚያ ህመሞች ላይ ትኩረት አድርጎ የተደራጀው “የሩማቶሎጂ እና የውስጥ ደዌ ህክምና አገልግሎት በትናንትናው እለት ጀምሯል።በግል የህክምና ተቋማት ደረጃ የመጀመሪያ ነው የተባለለት የመገ…

https://cdn4.telegram-cdn.org/file/O4dJbdrEKr41JMkvrEeJfzWafScxIRJqml_XnPdYS1acCSUeAnzUpVcoG1JpbUxOc36g5q9BTeDViX7rHBSJHhvjWRTxe66BUHof50KKxwwlgQ4Sj2zBofJBCF4eR_bSZ_NjSZeFGGgviwZieNYb7wEdI6eD8WyfwcQPEzQl7Itfqzie4kWrwr2JtJODMNNNspywlLRSk2PgF-7_9azAWhaMdPZrFNzYv5XkL3Zvbf00aO2bHJEUEZy-4QHTpL_aP6RJy059pes93mM6M5dcxwa8qvpAoYiHtqP0zNsp1c9WiayiX4CEiFKkghR7nKtJproF_owQBEcbf8kJUVgbRg.jpg

የመገጣጠሚያ ህመሞች ላይ ትኩረት አድርጎ የተደራጀው “የሩማቶሎጂ እና የውስጥ ደዌ ህክምና አገልግሎት በትናንትናው እለት ጀምሯል።

በግል የህክምና ተቋማት ደረጃ የመጀመሪያ ነው የተባለለት የመገጣጠሚያ ህመም ህክምና በሩሁም የሩማንቶሎጅ እና የውስጥ ደዌ ህክምና ስፔሻሊስት ክሊኒክ መሰጠት ተጀምሯል ።

በአለማችን 1.6 ቢሊየን የሚሆኑ ሰዎች የመገጣጠሚያ ህመም በሽታ ተጠቂ እንደሆኑ የክሊኒኩ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶከተር ብርሃኑ ደመላሽ ተናግረዋል ።

በተጨማሪም በሽታው ወደ ሃገራችን ሲመጣ ከ20 ሚሊየን በላይ የሚሆኑ ሰዎች በዚህ በሽታ እንደሚጠቁ ዳይርክተሩ ገልጸዋል ።

ይህንን በሽታ ለመቀነስ እና ለመከላከል እንዲያስችል “ሩሁም የሩማንቶሎጂ እና የውስጥ ደዌ ህክምና ክሊኒክ ” ህክምናውን ለመጀመሪያ ጊዜ በሃገራችን ጀምሯል ብለዋል።

በሃገራችን በበሽታው ላይ ከፍተኛ የሆነ የግንዛቤ እጥረት አለ ሲሉ የክሊኒኩ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ብርሃኑ ደመላሽ አንስተዋል ።

ከዚህም የተነሳ በቀላሉ መቀረፍ የሚችሉ የመገጣጠሚያ በሽታዎች ፣ወደ ልብ፣ ጭንቅላት ፣ወደ ኩላሊት፣ ወደ ነርቭ እና ወደተለያዩ በሽታዎች ይሸጋገራሉ ብለዋል።

ስለሆነም የህክምናውን ተደራሽነት በማስፋት በሰዓታት ውስጥ ሊስፋፋ የሚችለውን “የሪህ ወይም የመገጣጠሚያ ” በሽታን ለመከላከል ማእከሉ ወደ ስራ መግባቱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል ።

“ሩሁም ክሊኒክ” ይህን ህክምና አገልግሎት በአግባቡ መስጠት እንዲያስችለው በቂርቆስ ታቦት ማደሪያ አካባቢ የቂርቆስ ቴሌ አጠገብ የህክምና ማእከል መክፈቱን አስታውቋል ።

በመሳይ ገ/ መድህን

Source: Link to the Post

Leave a Reply