
የምስራቅ አማራ ፋኖ በራያ ቆቦ ታላቅ የዝክረ ሰማዕታት ዝግጅት እንደሚኖረው አስታወቀ። አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ ሸዋ ለአገራችን ኢትዮጵያ እና ለአማራ ህዝብ ታላቅ መስዋዕትነት የከፈለው ምስራቅ አማራ ፋኖ ታህሳስ 2/2015 ዓ.ም ዝክረ ሰማዕታት እና አጠቃላይ የትግል ጉዞ መታሰቢያ ዝግጅት ራያ ቆቦ ላይ አዘጋጅተናል ብሏል፡፡ በዚህ ዝግጅት የአማራ ህዝብ የፍትህ የዕኩልነት እና የነጻነት በአጠቃላይ የህልዉና ትግሉ የሚመለከተው ሁሉ እንዲሳተፍ በአማራ ፋኖ ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ብሏል፡፡ “ፋኖነት ለኢትዮጵያዊነት ህያው ምስክር ነው፡፡”
Source: Link to the Post