
የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት የሰላም ስምምነቱ የሚጠይቀውን ሁሉ ተግባራዊ እያደረኩ ነው እያለ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ ከትግራይ በኩል ግን መንግሥት ቃሉን ሙሉ ለሙሉ እያከበረ አይደለም የሚል ወቀሳ እየተሰነዘረ ነው። መንግሥት ቅዳሜ ታኅሣሥ 08/2015 ዓ.ም. በኮሙኒኬሽን ጉዳዮች አገልግሎቱ በኩል ባወጣው መግለጫ ላይ የተደረሰውን ስምምነት ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጾ የነበረ ቢሆንም፣ በህወሓት በኩል ግን ከዚህ የሚቃረን ሃሳብ ተሰንዝሯል።
Source: Link to the Post