
የትራፊክ ቅጣትን ለማሻሻል የሚያስችል አዲስ ጥናት እየተካሄደ ነው ተብሏል፡፡
ጥናቱ አሁን በሃገሪቱ እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋ በተሻለ ሁኔታ ለመቀነስ እንደሚያግዝ፣ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ተወካይ አቶ መኳንንት ምናሴ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።
80 በመቶ የሚሆነው የትራፊክ አደጋ የሚከሰተው በአሽከርካሪዎች ስህተት ምክንያትነት እንደሆነ የሚናገሩት አቶ መኳንት፣ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የትራፊክ ቅጣት ላይ ማሻሻያ ማድረግ ማስፈለጉን ገልጸዋል።
ከፍጥነት ወሰን በላይ የሚያሽከረክሩ አሽከርካሪዎችን ለመቆጣጠር በራዳር የታገዘ የፍጥነት ወሰን ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝም አንስተዋል፡፡
አሽከርካሪዎች ጥፋተኛ ሆነው ሲገኙ ቢቀጡም መሻሻሎች ባለመኖራቸው፣ ተጨማሪ ለውጥ የሚያመጡ ጥናቶች መጀመራቸውን ነግረውናል።
በጥናቱ ላይ የትራንስፖርት ሚኒስቴር፣ የትራንስፖርት ቢሮ፣ የመንገድ ድህንነት ፈንድ እንዲሁም የትራፊክ ማኔጅመንት አጀንሲ ተሳታፊ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በእሌኒ ግዛቸው
ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ.ም
ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ።
YouTube
https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA
Source: Link to the Post