
በትግራይ የተቀሰቀውን ጦርነት ተከትሎ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በትግራይ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት መካከል የነበረው ግንኙነት ሻክሯል። በቅርቡም የትግራይ አባቶች ኤጲስ ቆጶሳትን እንደሚሾሙ አስታውቀዋል። በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ደግሞ ከትግራይ አባቶች ጋር የተቋረጠውን ግንኙነት ለማደስ አስፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ አዟል። በትግራይ አባቶች በኩል ያለውን አቋም ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ ገልጸዋል።
Source: Link to the Post