You are currently viewing የአማራ ወጣቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወጣት ሰሎሞን ልመንህ በገዢው ቡድን አፋኝ የፀጥታ አካላት  መታፈኑን አረጋግጠናል ሲል የአማራ ወጣቶች ማህበር (አወማ) አስታወቀ ‼️ መጋቢት 26 ቀን…

የአማራ ወጣቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወጣት ሰሎሞን ልመንህ በገዢው ቡድን አፋኝ የፀጥታ አካላት መታፈኑን አረጋግጠናል ሲል የአማራ ወጣቶች ማህበር (አወማ) አስታወቀ ‼️ መጋቢት 26 ቀን…

የአማራ ወጣቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወጣት ሰሎሞን ልመንህ በገዢው ቡድን አፋኝ የፀጥታ አካላት መታፈኑን አረጋግጠናል ሲል የአማራ ወጣቶች ማህበር (አወማ) አስታወቀ ‼️ መጋቢት 26 ቀን 2015 ዓ.ም አሻራ ሚዲያ ፣ የአማራ ወጣቶች ማህበር የአደረጃጀት ጉዳይ ስራ አስፈፃሚ ወጣት ሰለሞን ልመንህ በቀን 22/07/2015 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ከሌሊቱ 5:00 ሰዐት ላይ የፀጥታ ልብስ በለበሱ ሰዎች ታፍኖ መወሰዱን እና ሜኪሲኮ አካባቢ በሚገኘው የገዢው ቡድን ማጎሪያ ካምፕ እንደሚገኝ መረጃ ደርሶናል ። የአማራ ወጣቶች ማህበር ባደረገው የተወሰነ የማጣራት ተግባራት የስራ አሰፈፃሚ አባላችን ያለበት ሁኔታ እጅጉን ያሳስበናል ።በቅርብ ቤተሰቦቹ ላይ የደረሰው ያለበትን ሁኔታ አለማወቅ የተፈጠረ እጅግ ዘግናኝ እና አስቸጋሪ ስነ – ልቦናዊ የመረበሽ ስሜት ውስጥ እንደሚገኙ አረጋግጠናል ።ይህ ግፍ ተገቢ ያልሆነ ፣የስርዓተ መንግስቱ አማራ ጠልነት አንዱ እና ትንሹ ማሳያ ነው ። በማሰር ፣በማዋከብ የሚቆም የአማራ ትግል የለም ።የትግላችን መዳረሻ የአማራ ህዝብ ነፃነት ነው ። ህልውናችን በክንዳችን‼️ የአማራ ወጣቶች ማህበር (አወማ) “ውድ የአሻራ ሚዲያ ቤተሰቦች የአሻራ ሚዲያ ቻናልን ላይክና ሰብስክራይብ በማድረግ ድጋፋችሁን ታሳዩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።” ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች አሻራ ሚዲያ የአይበገሬዎቹ ልሳን:- // Youtube:- https://www.youtube.com/channel/UCPmgFzP2ZPmdGjHxXjigJaw // Facebook:- https://www.facebook.com/asharamedia24 // ቴሌግራም:- https://t.me/asharamedia24

Source: Link to the Post

Leave a Reply